Announcement በተፈሪ መኮንን ፖ/ቴ /ኮሌጅ ታላቅ የስራ እድል ትስስር (Job Fair) ተካሄደ።

በተፈሪ መኮንን ፖ/ቴ /ኮሌጅ ታላቅ የስራ እድል ትስስር (Job Fair) ተካሄደ።

16th July, 2026

በቅርቡ መቶኛ አመቱን ያከበረው እና አለምአቀፉን የ የ ISO 210001 የጥራት ሰርትፍኬት ያገኘዉ አንጋፋው ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለሰልጣኞች የስራ ትስስር ለመፍጠር በርካታ ተቋማት የተሳተፉበት አውደ ርዕይ አዘጋጀ ።
በዕለቱም የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ሀላፊ ወ/ሮ ዳግማዊት ግርማ ፣ የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ፣ ከተለያዩ የቴ/ሙ የመጡ የኮሌጅ ዲኖችና አመራሮች ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶችና ከ30 በላይ ቀጣሪ ድርጅቶች ተገኝተዋል ።
መርሀግብሩ ተመራቂ ተማሪዎችን በቀጥታ ከቀጣሪዎቻቸው ጋር ለማገናኘት ታስቦ የተዘጋጀ ሲሆን ሰልጣኞች የክህሎት ልውውጥ በማድረግ በተለያዩ የስራ ዘርፎች ማለትም በሆቴል ፣ በአይሲቲ ፣ ፋይናንስ ፣ ኤሌክትሪክ እና እንጨት ስራ አምራቾች ፣ አረንጓዴ ቴክኖሎጅ ፣በጋርመንትና ፣ በሌሎች የሙያ ዘርፎች ላይ ከሚሰሩ ተቋማት ጋር እንዲገናኙ እድሎች ተመቻችተዋል።
በቀጣይም እንዲህ ያሉ የስራ ትስስሮች በቋሚነት እንደሚደረጉ የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ በተደረጉት ግንኙነቶች በርካታ ሰልጣኞች የስራ እድል እንዳገኙም ገልፀዋል። ዲኑ አክለዉም ይህ ሁነት እንዲዘጋጅ የተባባሩ አካላትን በተለይም ደግሞ EASE ፕሮጀክትን በተለየ ሁኔታ ያመሰገኑ ሲሆን ይህ ሁነት በቀጣይም በስፋት እንደሚደረግ ገልጸዋል።
.

Copyright © All rights reserved.

Created with